


የትምህርት ቤታችን አጭር ታሪክ
የኮን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ወረዳ የሚገኝ ትምህርት ቤት ነው። ትምህርት ቤቱ በ 1945 አ.ም ተቋቋሞ እስከ አሁን ድረስ ተማሪዎችን እየተቀበለ ለትልቅ ደረጃ ሲያደረስ የቆየ እድሜ ጠገብ አንጋፋ ትምህርት ቤት ነው። ላለፉት 73 አመታት በቁጥር ይህ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የማይችል በትምህርታቸው ሃገራቸውንና ወገኖቻቸውን የረዱና እየረዱ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ማፍራት የቻለ በክልሉ ከሚጠቀሱ ዝነኛ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። ይህን ትምህርት ቤት ከሌሎች መሰል ትምህርት ቤቶች ለየት የሚያደርገው ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ከተለያዩ ወረዳዎች እንዲሁም በወረዳው ውስጥ ካሉ ከ25 የሚበልጡ ቀበሌዎች የሚመጡ ተማሪዎችን እየተቀበለ ያስተማረና እያስተማረ የሚገኝ መሆኑ ነው።

ፋውንዴሽናችን እንዴት ተጀመረ
ትምህርት ቤቱ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ማለትም የትምህርት ፋሲሊቲዎች (ግብአት) በበቂ ሁኔታ አለመኖር እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርት አለመሰጠት ተማሪዎች ከሌሎች ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ እንቅፋት ሆኖ ቆይተዋል። ስለዚህ እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች በመገንዘብ የኮን ሃይስኩል ፋውንዴሽን ማቋቋም እንደ መፍትሔ ታቅዶ በትልቅ ራእይ የተጀመረ ፋውንዴሽን ነው። ስለሆነም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር፣ በዚሁ ትምህርት ቤት ተምረው ትልቅ ደረጃ የደረሱ የቀድሞ ተማሪዎችን በመያዝ እንዲሁም ዓላማችን በመደገፍ ተባባሪ በመሆን የበኩላቸውን ኣሻራ ለማሳረፍ ፈቃደኛ በሆኑ ቅን ልቦና ባላቸው ግለሰቦችን ጭምር በማካተት የመፍትሔ አካል እንዲሆኑ አድርጎ ስራውን ጀምሯል።
ዋና ዋና የትኩረት መስኮች
በእነዚህ ቁልፍ መስኮች ላይ በማተኮር ዘላቂና አዎንታዊ ለውጥ ለማምጣት እንጥራለን።
የትምህርት ግብአቶች
የትምህርት ግብአቶችን አቅም በፈቀደ መጠን በማቅረብ የተማሪዎችን የመማር ሂደት እናግዛለን።
ዘመናዊ ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት
ተማሪዎችን ከዘመኑ የትምህርት ስርአት ጋር ጎን ለጎን እንዲሄዱ በዲጂታል የታገዘ የላይብረሪና ተጨማሪ ነፃ የኦንላይን ኮርሶችን እንዲያገኙ ማድረግ።
ለተማሪዎች ድጋፍ
የአቅም ውስንነት ያለባቸውን ተማሪዎችን በመደገፍ የትምህርት ህልማቸው እውን እንዲሆን ማድረግና መከታተል።
የተጀመረውን እንቅስቃሴውን ይቀላቀሉ
የእርስዎ ድጋፍ በቀጥታ የተማሪዎችን ህይወት ይለውጣል። ምን ያህል እንደተጓዝን እና ግባችንን ለመምታት ምን ያህል እንደቀረን ይመልከቱ። ( የገንዘብ ቻርት ላይ የሚታየው ቁጥር በገንዘብ ከተለገሰው በተጨማሪ በማቴርያል ድጋፍ ከተገኘውም ዋጋ ሰነድ ላይ ወደ ገንዘብ በመቀየር የተጨመረ ሊሆን ይችላል። )
+
ተማሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል
ቤተ-መጻሕፍት ተደግፈዋል
+
መጻሕፍት ገቢ ተደርጓል
+
የትምህርት አይነቶች ተሸፍነዋል
ድጋፍ ያደረጉ ሰዎች
የምስራች
በዌብሳይታችን ያካተትናቸው ትልቅ ፍሬ የምንጠብቅባቸውን ገጽኦች እናስተዋውቃችሁ፡
ነፃ የኦንላይን ትምህርቶች
ዲጂታል ላይብራሪ
በቅርብ የሚጀምር
ነፃ የኦንላይን ትምህርቶች
በአሁኑ ጊዜ ተመራጭ በሆኑና እንደ ሃርቫርድ ባሉ ታላላቅ በሚባሉ ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጡ ማንኛውንም ነፃ የኦንላይን የትምህርት እድል እንድታገኙ ፋውንዴሽናችን አመቻችቷል።
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች
ከፋውንዴሽናችን ጋር የተያያዙ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ዝግጅቶችን ይከታተሉ።
June 15, 2025
በሰሜን ወሎ ዞን በዋድላ ወረዳ ለኮን 2ኛና መሰናዶ ትምህርት ቤት ከ65ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ መጽሀፍት ድጋፍ ተደረገ።
ድጋፉ የተደረገው የቀድሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪና መምህር በነበሩት በአቶ ሰለሞን ይመር ነዋሪነታቸው በአሜሪካን ሀገር ሲሆን በዛሬው ዕለት ለኮን 2ኛና መሰናዶ ትምህርት ቤት 1መቶ 34 መጽሀፍት ከ65ሺህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ ገዝተው በቀድሞ ጓደኛቸውና በትምህርት ቤቱ መምህር አቤል ቢሰጠኝ በኩል በሚመለከታቸው አካላት አማካኝነት ርክክብ ተደርጓል።
Read on Facebookለውጡን ዛሬውኑ ይቀላቀሉ!
የእርስዎ ተሳትፎ፣ በየትኛውም መልኩ ቢሆን፣ ትልቅ ለውጥ ያመጣል። የኮን ሃይስኩል ተማሪዎችን ህልም እውን ለማድረግ አብረን እንስራ።